ማስተማር . ማስታጠቅ . መላክ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት
ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት የቅዱሳት መጻሕፍትን ‘ትልቅ ስዕል’ መመልከት ነው። ይህም እያንዳንዱን ጥቅስ ወይም ታሪክ ለየብቻ ነጣጥለን ከማየት ይልቅ፣ ሁሉም ክፍሎች ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ተሳስረው እንዴት አንድ ወጥ የሆነውን የእግዚአብሔርን የድነት-ታሪክ የምናይበት መንገድ ነው። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ብሉይ ኪዳን እንዴት ከአዲስ እንደሚገጣጠም በማስተዋል፣ እግዚአብሔር በቃሉ በኵል ዛሬ ለእኛ የሚናገረውን መልእክት በግልጽ እንድነሰማ ይረዳናል።

በዚህ ድረ-ገጽ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በምናደርገው ጉዞ፣ ለህይወታችንና ለቤተ ክርስቲያናችን የሚሆኑ ጥልቅ እውነቶችን ለማስረዳት እንሻለን። ስለዚህ፣ ለቤተ ክርስቲያን ይህንን ወሳኝ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ ልናስተዋውቃችሁ እንወዳለን። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ለነገረ-መለኮት መምህራንና ተቋማት ብቻ የተሰጠ ሳይሆን፣ ለቤተ ክርስቲያን መታነጽና ለእያንዳንዱ አማኝ የሚጠቅም ኀይለኛ መሣሪያ እንደሆነ አንጠራጠርም።

ማስተማር . ማስታጠቅ . መላክ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት
ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት የቅዱሳት መጻሕፍትን ‘ትልቅ ስዕል’ መመልከት ነው። ይህም እያንዳንዱን ጥቅስ ወይም ታሪክ ለየብቻ ነጣጥለን ከማየት ይልቅ፣ ሁሉም ክፍሎች ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ተሳስረው እንዴት አንድ ወጥ የሆነውን የእግዚአብሔርን የድነት-ታሪክ የምናይበት መንገድ ነው። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ብሉይ ኪዳን እንዴት ከአዲስ እንደሚገጣጠም በማስተዋል፣ እግዚአብሔር በቃሉ በኵል ዛሬ ለእኛ የሚናገረውን መልእክት በግልጽ እንድነሰማ ይረዳናል።

በዚህ ድረ-ገጽ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በምናደርገው ጉዞ፣ ለህይወታችንና ለቤተ ክርስቲያናችን የሚሆኑ ጥልቅ እውነቶችን ለማስረዳት እንሻለን። ስለዚህ፣ ለቤተ ክርስቲያን ይህንን ወሳኝ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ ልናስተዋውቃችሁ እንወዳለን። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ለነገረ-መለኮት መምህራንና ተቋማት ብቻ የተሰጠ ሳይሆን፣ ለቤተ ክርስቲያን መታነጽና ለእያንዳንዱ አማኝ የሚጠቅም ኀይለኛ መሣሪያ እንደሆነ አንጠራጠርም።

ትኩረታችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ነው

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ለአጥቢያ ቤተክርስቲያን እንደሆነ እናምናለን። ይህ ጥናት የአእምሮ እውቀት ብቻ አይደለም። ይልቁንም፣ ለአማኞች በተናጠልና ለቤተ ክርስቲያን ህይወት በጥቅል አያሌ ተግባራዊ ጠቀሜታ አለው። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት፣ ባለ ብዙ ገጽታና አስደናቂ ባለጠግነት ባለው ቃሉ ውስጥ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ዐሳብ እንድናይ በማድረግ ሕይወታችንን ይለውጣል።

ወንጌልን ግልጽና አንድ ወጥ ያደርገዋል | It makes the Gospel coherent
እምነታችንንና ተግባራችንን ይቀርጻል | It shapes our faith and practice
በቃሉ ላይ እንድንመሠረት ያደርገናል | It keeps us grounded in the text
እውነትን በማስተዋል እንድንተገብር ይረዳናል | It helps us apply truth thoughtfully
መጽሐፍ ቅዱስ ለእኛ እንደተሰጠ አበክሮ ያሳስበናል | It reminds us that the Bible is for us
የእግዚአብሔርን ባህሪና ሥራ ይገልጥልናል | It reveals God’s nature and actions

በመጨረሻም በክርስቶስ እና በመንፈስ ቅዱስ በኩል ለተሰጠንና ሥልጣን ላለው የእግዚአብሔር መገለጥ በትህትና ምላሽ እንድንሰጥ ያበረታታናል። ሁላችንም በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት በዕውቀት እናድግ ዘንድ፣ ይህም ለእግዚአብሔር ቃል ያለንን አክብሮት እንዲያቀጣጥልና ከእርሱ ጋር ያለንን አካሄድ እንዲያጠነክርልን ምኞቴ ነው!

Available Courses

The Speaking God: Biblical Theology & The Storyline of Scripture.
Cruciform Ministry: The Call, Character, and Competence of a New Covenant Minister (Studies in 2 Corinthians).
Rightly Dividing the Word: Principles of Biblical Hermeneutics.
The Kingdom Manifesto: Living Out the Sermon on the Mount.

What Else is Important?

Tailored Content: We can adjust the focus of the teaching to address specific needs or challenges your local church is currently facing.
Interactive Learning: These are not dry academic lectures. We prioritize Q&A, engagement, and prayerful reflection.
The Goal: Our ultimate aim is not just knowledge transfer, but to ignite a passion for Christ and His Church.

እየተሰጡ ያሉ ትምህርቶች

Currently, we are opening up the following teaching series. If your church would like to host one of these classes, please contact us.

Equip Your Church with Deep, Life-Changing Theology.

Recover the Authority of Scripture: Move beyond basic reading to encountering the “Speaking God” and seeing the unified story of Redemptive History.
Redefine Success in Ministry: challenging the “celebrity” culture of modern ministry with Paul’s “Cruciform” model of service, humility, and power in weakness (2 Corinthians).
Empower Your Leaders: Give your Sunday School teachers and small group leaders the practical tools they need to interpret and teach the Bible accurately (Hermeneutics).
Live the Kingdom Life: Help your congregation navigate the “upside-down” values of the Kingdom of God through the Sermon on the Mount.

Flexible Formats to Fit Your Schedule

2-Hour Workshop: A high-impact overview of a specific topic (perfect for evening sessions).
4-Hour Half-Day Seminar: Deep dive into key concepts with interaction (great for Saturday mornings).
8-Hour Full-Day Intensive: Comprehensive training with extensive practice and Q&A (ideal for leadership retreats).

What You Get

Well-Organized Teaching Series: Structured, theological, and practical content.
Handouts & PowerPoint Materials: Visual aids and notes for attendees to keep.
Group Discussions & Study Materials: Interactive questions to facilitate peer learning.
Practical Exercises: (For the Hermeneutics/Bible Study courses) Real-time practice in interpreting texts.

የሚናገረው አምላክ፡ የቅዱሳት መጻሕፍት ሥልጣንና መሠረታዊ ባሕርይ

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን በጥያቄ ምልክት ውስጥ በገባበትና ብዥታ በበዛበት በዚህ ዘመን፣ ቤተክርስቲያን ወደ እውነተኛው መሠረቷ መመለስ አለባት። ይህ ሴሚናር ከተለመዱት የአጠናን ዘዴዎች (Study methods) አልፎ፣ መጽሐፍ ቅዱስ “ምንድን ነው?” ወደሚለው መሠረታዊ የእግዚአብሔር ድምፅነት ይወስደናል።

የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናንና አተረጓጎም

(Biblical Interpretation)
የእግዚአብሔርን ቃል “በትክክል የሚያስረዳ” (2 ጢሞ 2:15) አገልጋይና አማኝ ለመሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት በትክክል እንደሚያዝ መረዳት ወሳኝ ነው። ይህ ሴሚናር ከዘልማዳዊ ንባብ ወጥተን፣ መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበትን ዐውድ፣ የሥነ-ጽሑፍ ዓይነት እና የቃላት ፍቺ በመመርመር፣ የጸሐፊውን ሐሳብ እንዴት ማግኘት እንደምንችል በተግባር የሚያስታጥቅ ነው።

ቅርጸ-መስቀላዊ አገልግሎት፡ የአዲስ ኪዳን አገልግሎት ጥሪና ክብር

በዘመናችን ስለ “አገልግሎት” ያለን ግንዛቤ በዝና፣ በገንዘብና በውጫዊ ስኬት መለኪያዎች ተበርዟል። ብዙዎች “ለዚህ አገልግሎት የሚበቃ ማን ነው?” ብለው ከመጠየቅ ይልቅ፣ በራሳቸው ብቃት እየተመኩ ወንጌልን ወደ ንግድ ሸቀጥነት (Peddling) የቀየሩበት ጊዜ ላይ ነን። ይህ ሴሚናር፣ ሐዋርያው ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ መልእክቱ ላይ እንደሚያስተምረው፣ አገልግሎት ማለት የግል ስኬት መሰላል ሳይሆን “የተሰቀለውን ክርስቶስን” በመስበክ ፣ አገልግሎታቸው የመስቀሉን ቅርጽ (Cruciformity) እንዴት መላበስ እንዳለበት በሰፊው ይዳስሳል።

የተራራው ስብከት

(The Sermon on the Mount)
“የተራራው ስብከት” የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ጫፍ እና የክርስትናዊ ሥነ-ምግባር መሠረት ነው።
ብዙዎቻችን እነዚህን ምንባባት (ማቴዎስ 5 – 7 ) ብናውቃቸውም፣ ወደ ጥልቀቱ ወርደን የመንግሥቱን የኑሮ ዘይቤ ምንነት ግን አልተረዳንም።
ይህ ሴሚናር፣ ኢየሱስ በምድር ላይ ሊመሠርተው ስለመጣው መንግሥት ባህርይ፣ ስለ እውነተኛ ጽድቅ እና ስለ ኪዳኑ ሕዝብ አኗኗር ያስተማረውን ሕያው ቃል የምንመረምርበት ነው።